tg-me.com/nibab_lehiwot/148
Create:
Last Update:
Last Update:
🕊️ሀሙስ🕊️
ክፍል-3
አዎ ልክ ነወት ግንኮ እነሱን መሆን መመኘቴ ምንም ክፋት የለውም።እውቀት አላቸው፣ ጥበብ አላቸው ፣ብዙ ነገር መስራት ይችላሉ ፣ደግሞም በጣም ትጉህ ናቸው።ታዲያ ለምን እነሱን መሆን አልሻም አልኩ በሙሉ የራስ መተማመን።
ፊታቸውን ፈገግ አደረጉት ከዛም ወዳያው ኮስተር አሉ።ጥሩ ነው ስለ እነሱ በደምብ ታውቂያለሽ እውቀታቸው የስርቆት ፣ ጥበባቸው የሰይጣን ፣ስራቸው በተንኮል ፣ትጋታቸው እኛን ስለማጥፋት....... መሆኑንስ ታውቂያለሽ ?
እኚህ ሰውየ እብድ ይሆኑ እንዴ ? ዘንድሮኮ ኑሮ ያላሳበደው የለም በማን መፍረድ ይቻላል? እያልኩ ከራሴ ጋ በውስጤ ሳወራ ለሳቸው መመለሴን ዘንግቸው ኖሮ........በድጋሚ እሽ ይሄን ተይው ኢትዮጵያዊ መሆንንስ አትመኚም ? አሉኝ በመገረም እየተመለከቱኝ።.......እንዴ ኢትዮጵያዊ ሆኜ ለምን ኢትዮጵያዊነትን እመኛለሁ።አልኩ ግራ በገባው አነጋገር።
ደግ ኢትዮጵያዊ ነኝ ብለሻል። በይ እንግዲህ ስለ ኢትዮጵያውያን ስራ ንገሪኝ ?ምን እንዳደረጉ ተርኪልኝ።መቸም የራሱን ሀገር ታሪክ የማያውቅ ዜጋ የለም።ስለዚህ በደምብ አስረጂኝ.........
ፈጣሪየ ሆይ በጣም ደነገጥኩ ።እኔ ሲጀመር ያለ ማጋነን ስለ ኢትዮጵያ ምንም አላውቅም። የማውቀው እንደምጠላት ብቻ ነው።
✍bee
BY ሕይወትን - በገፅ
Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283
Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/148